አልፈራም


Saturday, April 27, 2024

ለምን ለምን ሞተ ?! የሞተው ለኔ ነው !

 ለምን ለምን ሞተ ?! የሞተው ለኔ ነው !

TESFAYE HAILU B· APRIL 25, 2016· 4 MINUTE

ገባኝ ዝም ብዬ መስቀሉን አይቼ 

በፈሰሰ ደሙ ፈለግ ተመርቼ 

ፈለጉን ስከተል የደሙን ነጠብጣብ 

ቀራንዩ ደረስሁ ከመስቀሉ እርካብ 

ዐያለሁ ዐያለሁ መስቀሉን ዐያለሁ

ቀራንዬ ቆሜ መስቀሉን አያለሁ 

መስቀሉ ደም ለብሶ  

ችንካሩም ደም ጎርሶ 

ያበሳ ማህተም የሰቀቀን ቀለም ላዩ ታትሞበት 

በደንብ ያስታውቃል ጌታ እንደሞተበት 

እንዴት ለምን ሞተ አምላክ ሆኖ ሳለ 

ሰማይን የሰራው 

ምድርን የዘረጋው 

ለይኩን የሚለው .ያ ቃሉ እያለ

እኮ ለምን ሞተ … 

አምላክ ለምን ሞተ 

የአላዛር ትንሳኤ 

የሞት ሁሉ ጌታ 

እኮ ለምን ሞተ

ፀሐይ  እንድትጨልም 

ጨረቃ እንድትደማ  

መሬት እንድትዝል 

ኮከብ እንዲረግፍ … ከመሰለኝማ … 

አዚም ሸፍኖኝ ነው ….

ተረት ጋርዶብኝ ነው … 

የሞተው ለኔ ነው … ለኔ ለምስኪኑ 

ምስጢር ስተረትር … 

የሰው ህልም ስፈታ …

ለመሸብኝ ቀኑ … 

የሞተው ለኔ ነው … ለኔ ለጉስቁሉ … 

ፊደልን ሳዋድድ … 

ቅኔ ስፈበርክ … ለጠፋብኝ ቃሉ 

  

የሞተው ለኔ ነው 

አበሳዬን ሊያርቅ

ከገነት ሊያስገባኝ 

የሞላ ጎደለ ጫወታ ላዛለኝ 

ሃጢያት አኮስምኖኝ ጽድቄ ሁላ ጎድፎ 

ኢየሱስ በሞቱ አነሳልኝ ገፎ 

የሞተው ለኔ ነው … ለኔ ለድንብሩ 

አይዞህ ዘራፍ እያልኩ … 

ቀረርቶ እያሰማሁ ለጠፋሁ ከስሩ … 

የሞተው ለኔ ነው … ጉልበቴ ለከዳኝ 

ከዲብሎስ ፍልሚያ … 

ከሰይጣን ጦርነት ..በእጅጉ ላዛለኝ 

ሀይል ብርታት ሊሆነኝ … ፅድቄን ሊያሰምርንኝ 

ኢየሱስ አምላኬ … በፍቅር ሞተልኝ … 

የሞተው ለኔ ነው … ለኔ ለሰነፉ 

አለሁኝ ከቤትህ … 

አለሁ ከመቅደስህ … 

እያልኩ ለጠፋሁኝ … ሌሎቹም ሲጠፉ 

የመከራህ ቃላት ወንጌልህ ሲነገር 

መለኪያ የሌለው የፍቅርህ ዳር ድንበር 

መስማት እያቃተኝ … ሲቃ እያነቀኝ 

ለማን እንደምትሞት … 

ለምን እንደምትሞት … ነገሩ ሲገባኝ 

ሀዘን ከደስታ … 

ሀሴት ከምሬት ጋር … ድብልቅልቅ እያለ 

ልቤን ከጥግ ጥግ ያላጋት ጀመረ 

ለሞትህም ሙሾ … ለሞትህ እልልታ … 

አንተስ ትገርማለህ …ሁልግዜ ጌታ … 

የሞትከው ለኔ ነው … 

ግራ ቀኝ ለማላውቅ … ውሉ ለጠፋብኝ …

ገርበብ ያለ ሁሉ በሩን ለሚመስለኝ … 

እድሜዬን በሙሉ ሳንኳኳ ሳንኳኳ… እስኪላጥ መዳፌ 

ሞትህ በረገደው … እልልታ ላሰማ … ከሲኦል ባርነት ባንተ በመትረፌ 

የሞተው ለኔ ነው … ለኔ ለትንሹ 

ካፈር አበጅቶ … ነፍስን ለዘራብኝ … በቅዱስ ትንፈሹ …. 

የሞተው ለኔ ነው

No comments:

Post a Comment