ቁጣና በረከት …
ምስኪኑ የሰው ልጅ
መነጽር አድርጎ … ምድር ባፈራችው …
ዕይታውን ስቶ … ትርጉም ተገልብጦ … ዓለም .. ጉድ ሰራችው…
ሞቱን ሕይወት ብላ … ብትሰፍርለት ቆሎ …
የሰው ልጅ ተሞኘ … በረከት ነው ብሎ …
ድንገት ጉንፋን ብጤ … ቢይዘው ታመመ …
የእግዚአብሔር ቁጣ ነው … ብሎ ደመደመ …
….
በረከት አንዲት ናት … ያቺም … ልጁን ማግኘት
ቁጣውም አንድ ነው … እሱም … ልጁን ማጣት …. !
No comments:
Post a Comment