የ ኢየሱስ እንባ
አምላክ ሆኖ ሳለ … የዓለማት ፈጣሪ፣
ወደ ፍቅሩ ዙፋን … በሩን ከፍቶ ጠሪ፣
እኔን በሱ አምሳል … ሰራኝ ስል አምኘ፣
በኔ አምሳል ሆኖ … ሲያለቅስ ተገኘ።
እኔስ ያለቀስኩት … ለሞተው ወገኔ ፣
ሞትን ድል መንሳት … ስላጣሁኝ ወኔ።
እሱ ለአላዛር … ያለቀሰለት… ፣
እኔ እንደማልችል …
እሱ እንደሚችል … አምላኬ አውቆት!!
በቃልህ ሞረደኝ … በቃልህ አበርታኝ፣
እለት እለት ሁሉ … አንተን ሆኜ ልገኝ፣
ወደዛች የ እምነት ጥግ … ኢየሱስ ውሰደኝ፣
ድካሜን እያሰብኩ … ሳልቅስ አልገኝ!!
No comments:
Post a Comment