አልፈራም


Saturday, April 27, 2024

የ ኢየሱስ እንባ

 የ ኢየሱስ እንባ 

አምላክ ሆኖ ሳለ … የዓለማት ፈጣሪ፣ 

ወደ ፍቅሩ ዙፋን … በሩን ከፍቶ ጠሪ፣ 

እኔን በሱ አምሳል … ሰራኝ ስል አምኘ፣ 

በኔ አምሳል ሆኖ … ሲያለቅስ ተገኘ። 

እኔስ ያለቀስኩት … ለሞተው ወገኔ ፣ 

ሞትን ድል መንሳት …  ስላጣሁኝ ወኔ። 

እሱ ለአላዛር … ያለቀሰለት… ፣

እኔ እንደማልችል …

እሱ እንደሚችል … አምላኬ አውቆት!! 

በቃልህ ሞረደኝ … በቃልህ አበርታኝ፣ 

እለት እለት ሁሉ … አንተን ሆኜ ልገኝ፣ 

ወደዛች የ እምነት ጥግ … ኢየሱስ ውሰደኝ፣ 

ድካሜን እያሰብኩ … ሳልቅስ አልገኝ!!

No comments:

Post a Comment