አልፈራም


Saturday, April 27, 2024

ማህበራችንን አንተው !!

 ማህበራችንን አንተው !!


ክርስቶስ እኔ ነኝ ብዬ መናገሬ ... 

ለዝና አይደለም ለጉራና ወሬ ...

ከጉጉቴ ብዛት በፍቅሩ በፍቅሬ ...

በሚያስደንቅ ቃሉ በመንፈስ ሰክሬ ... 

ራሴን ከአብቀኝ በድንገት አግኝቼው ...

ማማ መወጣጫው ለካ መስቀሉ ነው ... 

ሞት የሚገባው ሰው በነጻ ተለቆ ... 

የማምይሞተው ሞቶ በኔ በደል ደቆ ... 

እኔን ስለሞተኝ ....  

ከመናገር በላይ ቃሉ ጠጥሮብኝ ... 

አምላክ እኔ ሆንኩኝ ...ከቶ እንዳይመስልብኝ!! 

አደራ !

እውነት እና ሃቁ ... ክርስቶስ እኔን ነው ... 

በፍቅር ተስቦ ... 

እርሱ እኔን ሆኖ ... ሞቴን ስለሞተ ... 

ሃጢያቴ በሱ ... ስለተከተተ .... 

ጻድቅ ሆኖ ሳለ ... አምላክም ፈጣሪ ... 

አምላክ ልሁን ሳልል ... የሁሉ ጀማሪ ... 

በሞቱ ልመስለው ... ጅምር ሰው ሆኛለሁ ... 

በቃሉ ታንጬ ... ሙሉ ሰው ለመሆን ... ጉዞ ጀምሪአለሁ

በትንሳኤው ቆሜ ... እርሱን መስያለሁ ... 

በአብ ቀኝ እንዳልሁ ... እርሱን ተመልክቼ ይህን አምኛለሁ። 

ይኼ ሁሉ እምነት ... የእንቧይ ካብ እንዳይሆን 

በምግባር በርትተን ... እንድንተናነጽ 

ቃሉን ምግብ አርገን ... በሕብረት እንሁን!!

No comments:

Post a Comment