አልፈራም


Saturday, April 27, 2024

ባለአንድ መክሊቱ

 ባለአንድ መክሊቱ 


ለኔ ነው የሰጠው፣ ... አንዷን መክሊት መርጦ ...

አስር በተሰጠው ... አምስት በተሰጠው ... ከፍቅሩ ሳያጎድል ... እንደውም አብልጦ  

ዘርዝሬ ሳልበላት ... ወይ ሳልነግድባት  ... እንዲሁ አስቀምጬ  

ሌላው እንዳይወስዳት ... ቀብሬያት ከመሬት ... ሳልለውጣት ሸጬ 

እንዲሁ ደሃ ሆኜ ... አምላኬን ሳማርር ... እንዲገድለኝ ስመኝ ... ሰማይ ላይ አፍጥጬ 

አምጣ ያቺን መክሊት ... ሲለኝ ደጉ ጌታ ... በቁጣው መበርታት ... ባንኜ ደንግጬ 

ሳይዘራ የሚያጭድ ... ሳይበትን ሰብስቦ ... 

ጨካኝም መሆኑን ... ልቡናዬ አስቦ ... 

እነሆ መክሊትህ ... አልጠፋችም አለች ... ብየ ባስረክበው  

አውጡት ወዲያ ጣሉት  ... መክሊቱን ንጠቁት ... አስር ላለው ስጡት 

ብሎ ከመንግስቱ አስወጥቶ ጣለኝ ... 

አትርፎ ማይገኝ ... ሰነፍ ሃኬተኛ ... መሆኔ በደለኝ። 

አሁንማ ነቃሁ ... 

ዛሬ በምህረቱ ... ደግም ጠራኝና ... 

አንዱን ድንቅ መክሊት ... ልጁን ሰጠኝና ... 

በል ሂድ ተሰማራ ... ለዓለም ተናገር .. ይህን ወንጌል መስክር ...

እልፍ አኧላፍ አፍራ ... ትረፍና ብዛ  

በዚህ ድንቅ መክሊት ... የሰውልብን ግዛ !!

ብሎ ስላዘዘኝ ... 

ይኸው ለጌታዬ መልካሙ ባሪያ ነኝ!!

No comments:

Post a Comment