አልፈራም


Saturday, April 27, 2024

ሕይወትና ኑሮ ሲቀላቀሉብኝ፣

 ሕይወትና ኑሮ ሲቀላቀሉብኝ፣

 

ሕይወት ከባድ ሆነ ኑሮ ተወደደ፣ 

እያልኩ አወራለሁ፣ 

ሕይወት የሆነኝን ውስጤ የገባውን

ሕይወቴን ካላየሁ። 

ሕይወቴን ሳየው ግን … ቃሉን ስፈትሸው፣ 

ኑሮም እንደእምነቴ … ሕይወቴም ጌታ ነው።  


“አሁንም በሥጋ የምኖርበት ኑሮ በወደደኝና ስለ እኔ ራሱን በሰጠው በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ባለ እምነት የምኖረው ነው።” ገላ 2: 20

No comments:

Post a Comment