ግጥሞች አጫጭር ልብወለዶች ወጎችና ትዝታዎች
ሕይወትና ኑሮ ሲቀላቀሉብኝ፣
ሕይወት ከባድ ሆነ ኑሮ ተወደደ፣
እያልኩ አወራለሁ፣
ሕይወት የሆነኝን ውስጤ የገባውን
ሕይወቴን ካላየሁ።
ሕይወቴን ሳየው ግን … ቃሉን ስፈትሸው፣
ኑሮም እንደእምነቴ … ሕይወቴም ጌታ ነው።
“አሁንም በሥጋ የምኖርበት ኑሮ በወደደኝና ስለ እኔ ራሱን በሰጠው በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ባለ እምነት የምኖረው ነው።” ገላ 2: 20
No comments:
Post a Comment