እምነት ያለው ሰው አይፈራም …
ጦር ቢሰበቅ … ቢጎሰምም ሺኅ ነጋሪት
ህዝብ በህዝብ ቢነሳሳ … ቢታጠቅም እልፍ ሰራዊት
ሀገር መልኩ ቢደበዝዝ … ካርታው ቢፋቅ ከቀለሙ
የማንነት ስር መሰረት … አይጎመዝዝ መቼም ጣሙ
የዘር ነገር ቢመትሩት … ቢለኩትም ቢጎትቱት
ካዳም መቼም አልፎ አያውቅ … በወርቅ ሚዛን ቢመዝኑት
ቃል ነው ና የጣር ዘመን መጀመሪው … ቸነፈሩ ያስተጋባው
ህዝብ በ ህዝብ የተነሳው
የጦር ወሬ የሚሰማው
የሽብርወግ የሚናኘው … ካልሞቱት ነው አለን ብለው ከሚዋሹት፣
ወገኔ ሆይ …
ከኛ መንደር ግን ሰላም ሞልቷል
ከኛ መንደር አዳም ሞቷል፣
ዘርማንዘሩ አፈር በልቷል፣
አዲሱን ሰው ለብሰናዋል … እንደዚህ ነው የምናምነው፣
ለዚህም ነው የምንቆመው፣
እምነታችን ኃይል ያደርጋል …. እኛም ደግሞ እናምናለን
በአምላካችን በእግዚአብሔር … ከቤታችን ስለገባን፣
ምን አስፈራን !!
ስለዚህ
እምነት ያለው ሰው አይፈራም …
No comments:
Post a Comment