አልፈራም


Sunday, April 28, 2024

እንዲህ ነው ሳምንቱ ... ሕማማት

 

ሰኞ በለሲቱ ደረቀች ይላሉ ...

ጌታችን ቢረግማት፣  

ሳያገኝ ሲቀር .... ፍሬ ፈልጎባት።

ከኛም ፍሬ ሃይማኖት ... ጌታ እንዳያጣ ፣  

ወገባችን ታጥቆ ... መልካም ምግባር ያምጣ።

ጥያቄና መልሱ ... ማክሰኞ ነበረ፣

ጌታችን ሁሉንም ... ገልጦ ተናገረ።

አይሁድ ቅር አላቸው ...

አምላክ ነኝ ቢላቸው፣

ክፉ ስራቸውን ገልጦ ቢያሳያቸው፣  

ረቡዕ ቆረጡ ይሙት በቃ አሉ፣  

በቅናት ከሰሉ ... እጅግ ተቃጠሉ፣

ባካል ተገለጠ   ... ሐሙስ ትህትና

ጌታ እግር አጠበ ... ቸር አምላክ ነውና  

አርብ እለት ነበረ ... ጌታን የሰቀሉት፣

ሞቱስ ሕይወት ነበር ምስጢሩን ሳያውቁት።

በቀዳሚ ሰንበት መቃብር ቢያኖሩት፣

እሁድ ‘ለት ተነሳ እስቲ ምን ያድርጉት !!

No comments:

Post a Comment