አልፈራም


Saturday, April 27, 2024

በዮሃንስ ወንጌል በ ፲፯ ኛው አስደማሚ ምዕራፍ

 በዮሃንስ ወንጌል በ ፲፯ ኛው አስደማሚ ምዕራፍ 

ልቤ ተደመመ ቅኔን አፈለቀ በደስታ ዘረፈው ከመቅደሱ ደጃፍ  … 


ለአብ የነበርነው … ለወልድ ተሰጥተናል 

ሕይወት ስለሆነን …. ቃሉን ጠብቀናል 

ወልድ የያዘው ሁሉ 

የአብ እንደሆነ …. ጠንቅቀን አውቀናል 

ጌታም ስለእኛ …. መክበሩን አምነናል … 

ዓለም ገጭ ጓ ቢል … 

ከዓለም ሳንወጣ … በክንፎቹ ጥላ ከክፉ ተርፈናል 

ልጁን እንደጠላ … ዓለም ቢጠየፈን … ከቶ ምን ይደንቃል?

እኛም በክርስቶስ … ከአባቱ እልፍኝ … ላንወጣ ገብተናል 

ዓለም ሳይፈጠር … ለወልድ የተሰጠ … ያን ክብር አይተናል !! 

አሜን ተመስገን ነው ሌላ ምን ይባላል …

No comments:

Post a Comment