በዮሃንስ ወንጌል በ ፲፯ ኛው አስደማሚ ምዕራፍ
ልቤ ተደመመ ቅኔን አፈለቀ በደስታ ዘረፈው ከመቅደሱ ደጃፍ …
ለአብ የነበርነው … ለወልድ ተሰጥተናል
ሕይወት ስለሆነን …. ቃሉን ጠብቀናል
ወልድ የያዘው ሁሉ
የአብ እንደሆነ …. ጠንቅቀን አውቀናል
ጌታም ስለእኛ …. መክበሩን አምነናል …
ዓለም ገጭ ጓ ቢል …
ከዓለም ሳንወጣ … በክንፎቹ ጥላ ከክፉ ተርፈናል
ልጁን እንደጠላ … ዓለም ቢጠየፈን … ከቶ ምን ይደንቃል?
እኛም በክርስቶስ … ከአባቱ እልፍኝ … ላንወጣ ገብተናል
ዓለም ሳይፈጠር … ለወልድ የተሰጠ … ያን ክብር አይተናል !!
አሜን ተመስገን ነው ሌላ ምን ይባላል …
No comments:
Post a Comment