No lives matter …
ከ ኢየሱስ በቀር !!
ጥቁር ነብሱ ትብለጥ … ይከተላት ነጩ፣
እያለ ያውጃል … ዓለም ብልጭልጩ፣
አዋጁ የገባው … ሕይወት ያገኘ ሰው፣
የብርሃን ቀለም … ውስጡ የዘለቀው፣
ሲጮኹ አይጮህም … ያልፋል በአርምሞ፣
የሱን ሕይወት ክዶ … ባዲስ ህይወት ደምቆ … አምሮ ተሸልሞ።
ነፍስም ሆነ ስጋ … መንፈስና ሕይወት፣
የንቧይ ካብ ከንቱ … ነው ጌታ ከሌለበት፣
ነፍሱን የካደ ሰው … ሕይወትን የሚዋጅ፣
በጥቁር በነጭም … ራሱን ሳይፈርጅ፣
ብሎ ያመነ ሰው ..እኔ የእግዚአብሔር ልጅ፣
ቀለም አልባ ነብሱን … በጌታው ሰውሮ፣
የኢየሱስን ሕይወት … በራሱ ላይ ገልጦ … በድፍረት መስክሮ፣
መኖር ያኮራዋል … በአብ ቀኝ ባማረ … ከልጁ ጋር አብሮ !
No comments:
Post a Comment