አልፈራም


Saturday, April 27, 2024

ከ ኢየሱስ በቀር !!

 No lives matter … 

ከ ኢየሱስ በቀር !! 

ጥቁር ነብሱ ትብለጥ … ይከተላት ነጩ፣ 

እያለ ያውጃል … ዓለም ብልጭልጩ፣ 

አዋጁ የገባው … ሕይወት ያገኘ ሰው፣ 

የብርሃን ቀለም … ውስጡ የዘለቀው፣

ሲጮኹ አይጮህም … ያልፋል በአርምሞ፣ 

የሱን ሕይወት ክዶ … ባዲስ ህይወት ደምቆ … አምሮ ተሸልሞ። 

ነፍስም ሆነ ስጋ … መንፈስና ሕይወት፣ 

የንቧይ ካብ ከንቱ … ነው ጌታ ከሌለበት፣

ነፍሱን የካደ ሰው … ሕይወትን የሚዋጅ፣ 

በጥቁር በነጭም … ራሱን ሳይፈርጅ፣  

ብሎ ያመነ ሰው ..እኔ የእግዚአብሔር ልጅ፣  

ቀለም አልባ ነብሱን … በጌታው ሰውሮ፣ 

የኢየሱስን ሕይወት … በራሱ ላይ ገልጦ … በድፍረት መስክሮ፣ 

መኖር ያኮራዋል … በአብ ቀኝ ባማረ … ከልጁ ጋር አብሮ !  

No comments:

Post a Comment