አልፈራም


Saturday, April 27, 2024

ኢየሱስን ያዝኩት !!

 ኢየሱስን ያዝኩት !! 

ጠላቶች ሊገሉት ... ሊይዙት ፈለጉ፣ 

ወደሱ ቀረቡ ... እያፈገፈጉ፣  

ኑ ያዙኝ አለና ... 

በፈቃዱ ራሱን ... በጃቸው አኖረ፣ 

ይህን ታላቅ ምስጢር ... ማንስ መረመረ?  

እኔም ... 

ኢየሱስን ልያዝ ... ወገቤን ታጥቄ፣

መስቀል ተመርኩዤ ... ወንጌሉን ሰንቄ፣  

ልሰቅለው አይደለም ... ሕይወት ላረገው ነው፣ 

በኔ ፈቃድ ሳይሆን ... ሁሉ በሱ እኮ ነው። 

ኢየሱስ እንዲህ ነው ... 

አይደለም ልትይዘው ...

ልታምነው ስትፈልግ ... እሱ ካልፈቀደ፣ 

ያለሕይወት እምነት ... እያንገዳገደ፣

ሲቀርቡት ማፈግፈግ ... እየተለመደ፣ 

ስንት ዘመን ሄደ ... ስንት ቀን ነጎደ !!

በእምነት መኖር ነው ... እርሱን ሕይወት አርጎ፣

ሌላው ሁሉ ከንቱ ... ጌታን መያዝ በጎ።

No comments:

Post a Comment