ዓይኔ በርቶ

 የውስጥ ዓይኔ በርቶ ... የማየውም ካየኝ ... 

ምንጩ ጋ ከደረስኩ ... ቀድቶ መርካት እንጂ ... ከ'ንግዲህ ምን ቀረኝ ?

ታይቻለሁ ብዬ የማመኔ ምስጢር ፣ 

ብርሃን ነህ ብሎ ኢየሱስ ሲናገር፣ 

በጨለማ መሃል ብርሃን ስለሆንኩ፣ 

ታይቻለሁ ብዬ በ እምነት ተናገርኩ፣ 

የሚያየኝን እንዳየሁት የማየውም እኔን ካየኝ፣ 

ከእቅፉ መግባት እንጂ ... ከዚህ ዓለም ምንስ ቀረኝ ?

Comments

Popular Posts