ግጥሞች አጫጭር ልብወለዶች ወጎችና ትዝታዎች
የውስጥ ዓይኔ በርቶ ... የማየውም ካየኝ ...
ምንጩ ጋ ከደረስኩ ... ቀድቶ መርካት እንጂ ... ከ'ንግዲህ ምን ቀረኝ ?
ታይቻለሁ ብዬ የማመኔ ምስጢር ፣
ብርሃን ነህ ብሎ ኢየሱስ ሲናገር፣
በጨለማ መሃል ብርሃን ስለሆንኩ፣
ታይቻለሁ ብዬ በ እምነት ተናገርኩ፣
የሚያየኝን እንዳየሁት የማየውም እኔን ካየኝ፣
ከእቅፉ መግባት እንጂ ... ከዚህ ዓለም ምንስ ቀረኝ ?
No comments:
Post a Comment