አልፈራም


Saturday, April 27, 2024

ብርሃን ነኝ I am Light

 am Light 

ሃሳብና ልቤ፣ በሥጋ አእምሮ፣ በሚጮህ ሹክሹክታ፣ ያልተበጃጀሁኝ፤   

ድቅቅ ካልኩበት፣ ከብናኙ ቅንጣት፣ አፈር ከሚሆነው፣ ቀርጸው ያላኖሩኝ፤

ወገኔ የምለው፣ የሚሞተው ፍጥረት፣ በሕግ በስራቱ፣ አስተምሮ ያልዳኘኝ፤ 

የሰራሁት ሃጢያት፣ በደልና ወድቀት፣ዘር እያስቆጠረ፣ ሰብሮ ያላሰረኝ፣  

ልቤን እያወከ፣ ወገቤን አጉብጦ፣ ያስነከሰኝ ሕመም፣ አፌን ያልሸበበኝ፣  

የብዥታ ሕመም፣ የማይደረስ ሕልም፣ የቀቢጸ ተስፋ  ቅዠት ያልነጠለኝ፤  

በልጁ በየሱስ በሰማሁት ወንጌል፣ ብርሃን መሆኔን ማወጅ የጀመርኩኝ፣ 

ባካል በስጋዬ ደክሜ ምታዩኝ፣ 

በመንፈስ የምደምቅ ዛሬ ብርሃን ነኝ !!

No comments:

Post a Comment