የ ዮሃንስ ወንጌል
ከየኔታ’ግር ሥር … ከፊደል በኋላ… ድሮ ልጅ እያለሁ፣
ብስራተ አብ ብዬ … ወንጌል ቀጥያለሁ፣
ያኔ በንባብ ነው … በግዕዝ በ እዝል … በአራራይ ዜማ
የየሱስን ነገር … ሲተረክ ስሰማ፣
መች ገባኝ ነገሩ …
የ ሕይወት ሚስጥሩ …
መንገዱ እውነቱ …
የተፈታንበት … ከታሰርንበቱ፣
ብርሃን አይተናል በዚህ ቅዱስ ወንጌል፣
ብርሃን ውስጥ ገብተን ብርሃን ሆነናል፣
ከ እንግዲህ በኋላ ማን ይሸፍነናል።
No comments:
Post a Comment