አልፈራም


Saturday, April 27, 2024

ብስራተ አብ

 የ ዮሃንስ ወንጌል 

ከየኔታ’ግር ሥር … ከፊደል በኋላ… ድሮ ልጅ እያለሁ፣ 

ብስራተ አብ ብዬ … ወንጌል ቀጥያለሁ፣ 

ያኔ በንባብ ነው … በግዕዝ በ እዝል  … በአራራይ ዜማ 

የየሱስን ነገር … ሲተረክ ስሰማ፣ 

መች ገባኝ ነገሩ …

የ ሕይወት ሚስጥሩ … 

መንገዱ እውነቱ … 

የተፈታንበት … ከታሰርንበቱ፣ 

ብርሃን አይተናል በዚህ ቅዱስ ወንጌል፣ 

ብርሃን ውስጥ ገብተን ብርሃን ሆነናል፣ 

ከ እንግዲህ በኋላ ማን ይሸፍነናል።

No comments:

Post a Comment