አልፈራም


Saturday, April 27, 2024

ቅኔለሞት


ስለሞት ነው የምቀኘው ... ድል ተነስቶ በትንሳኤ፣ 

ይደልዎ እንዲል ካህን ... በሕማም ገጽ በጉባኤ።

አንዴ ሞቼ በክርስቶስ ... ከ'ንግዲማ መቼ ልሞት፣ 

የልጁ ሕይወት በሕይወቴ ... ሥጋ ነፍሴን አረስርሶት፣

አርባ አንድዱን ኪራላይሶን ... ለምን ልቁጠር ተደፍቼ፣ 

በልጁ ሞት ስለሞትኩኝ ... በትንሳኤው ተነስቼ፣ 

ንሴብሆ ልበል እንጂ ... በብርሃኑ ተሞልቼ።

No comments:

Post a Comment