እንዴት ማረኝ ልበል …
በአብ ቀኝ በኢየሱስ … ሆነና ሰፈሬ፣
ከማመስገን በቀር … ጠፋብኝ ነገሬ።
በሚያስደንቅ ፍቅሩ … በሞቱ ለወጠኝ፣
ሰው መሆን ተረሳ … ልጁም አደረገኝ።
አሁን …
የተማርኩ … ስለሆንኩ … በደል የሌለብኝ፣
ከአፌ ቃል ጠፋ … መናዘዝ አቃተኝ።
ከእቅፉ ገብቼ … ህልውናው ውጦኝ፣
ባዲሱ ማንነት … እንዴት ልበል ማረኝ?
ምናልባት ጸሎቴ … ሕይወት እንዲበዛ፣
አንድ ሰው እንዳይጎል … እንዲሁ እንደዋዛ።
ይህቺን ጸሎቴም … ምናልባት ካስታጎልኩ፣
በዚህ ዓለም ተውኔት … ምናልባት ከተሳብኩ።
አንድ ጋት ተስንዝር … ቁልቁል ለመራመድ.፣
ያሰብኩኝ እንደሆን …
ማረኝ እልሃለሁ … ተመልሼ እንዳልወርድ!!
No comments:
Post a Comment