ሃገሬ ሰማይ ነው !
የማለዳ አንቂ …
ያመርዶ ነጋሪ … ከቤቴ ቢመጣ፣
ሲፈራ ሲተባ …
ከደጄ ቆመና …
በል ልበስ ተነሳ …
ፊትክን አብስና .. ጋቢ ደርብና
ከመደብ ተቀመጥ … እርም እንድታወጣ፡፡
ሀገርህ ሞታለች …
በል ትፋ እርምህን … አንብቶ ሲያስነባኝ፣
እርሱ ..እያለቀሰ ..እኔን ሳቅ ከጀለኝ፡፡
ሀገሬ ሃገሬን … ሲዘፍኑ ስሰማ፣ …
ልቤ ልውስ ልውስ … ሆዴ ዠማ ዠማ፡፡ …
የሚል ነበር ድሮ …
ዘር የቆጠርኩ ቀን … ድንበር ያበጀሁ ለት …
ተወኝ … አትንገረኝ …
ሀገሬ ሌላ ነው .. አሁን ልረፍበት፡፡
ወገን ድንበር ይሉት …
ወንዝ ተራራ ጅረት …
ሞትም ሆነ መሞት …
ፓስፖርት የሌለበት …
ከገቡ ተከፍተው … ከቶ እማወጡበት ..
ሀገሬ ሰማይ ነው .. ግዛት የሌለበት …
አንደኛው ባንደኛው ... የማይነሳበት፡፡
No comments:
Post a Comment