አልፈራም


Saturday, April 27, 2024

መሄድና መምጣት

 መሄድና መምጣት 

፩. 

ወጥመድ ተሰበረ … ቅዠቱም ተፈታ፣ 

ሞራል ብርግድ ሲል … ጥያቄው በረታ። 

አጀንዳው ምንድነው … ነጥቡስ የቱ ነው? 

የትነው እምንሄደው እውነቱስ ከየት ነው? 

ማነው የጨቆነኝ ጭቆናስ ምንድነው? 

እያልን ስንጠይቅ … መልሱ ሁሉም ሆነ።  

፪.

እውነቱን እያወቅን ዓይናችን ተጋርዶ፣ 

ራስ ከእግራችን ባንድ ላይ ተገምዶ፣ 

ከተፈጥሮ እውነት … ብዙ ስለራቀ፣

የሰውልጅ ከራሱ … ራሱን ሰረቀ።

፫. 

መሃሉ ብርሃን መሃሉ ጨለማ፣

ራሱን ደብቆ ከውነት ሳይስማማ፣ 

ምስጢሩን ደብቆ .. ጠባሳውን ከቶ፣ 

ስሜቱንም ውጦ … ራሱንም ገቶ …

ሲወጣ ሌላ ነው … ሁሉን የሚወክል … ካባውም ዲሪቶ 

፬. 

ድራማው አንድ ነው … በእብደት የተኮላ፣ 

ውስጡ ባዶ ሲሆን … ውጪው እየሞላ፣ 

ይከታል ወደውስጥ … ሕይወቱ ተማርካ፣ 

በውድመት በጥፋት … ሚዛን እየለካ፣ 

፭. 

ታሪክ ስለሆነ … ሞራል መሰረቷ …. 

… እውነት የት አባቷ … 

ለመኖር ቢቃትት … ለውነት ቢሰናዳ፣

ሊሰብሩት ቢዘጋጅ … ሊታረድ ቢነዳ፣ 

አልገባ ስላለው …. 

በሰባራ ወጥመድ … መልሰው ሲከቱት.. 

ወጥመድ መስበሪያ ስልት … እዛ ውስጥ በራለት። 

አቤት !

No comments:

Post a Comment